ቪዲዮው አዲስ አይደለም። የፍልሰታ ሰሞን በፈረንጆች አቆጣጠር በ2009 የተቀረጸ ይመስላል። ቪዲዮው የሚያሳየው በኢየሩሳሌም ከተማ በምትገኘው ኪዳነ ምሕረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለ ሰላም ጸሎት ሲደረግ ነው። የሠርክ ጸሎትን አያይዞ የተደረገ ሥነ ሥርዓት እንደሆነ ለመረዳት ይቻላል። ቪዲዮው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ከተለያዩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ጋር በመሆን ለሰላም መቆሟን የሚያመለክት ነው። በተለይም የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ካህን በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተሳታፊ ሆነው ማየት ትልቅ ነገር ነው። ሊበረታታም የሚገባው እንቅስቃሴ ይመስላል።
ይህ ሁሉ መልካም ሆኖ ሳለ ቤተ ክርስቲያናችን ለዚህ የሰላም ጸሎት ተባባሪ ሆና ስትነሳ አንድ ማድረግ ያለባትን ነገር የረሳች ትመስላለች።