Wednesday, January 26, 2011

Prayer for Peace in our church in Jerusalem

Please follow the link below for a Prayer for Peace in our church in Jerusalem
ቪዲዮው አዲስ አይደለም። የፍልሰታ ሰሞን በፈረንጆች አቆጣጠር በ2009 የተቀረጸ ይመስላል። ቪዲዮው የሚያሳየው በኢየሩሳሌም ከተማ በምትገኘው ኪዳነ ምሕረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለ ሰላም ጸሎት ሲደረግ ነው። የሠርክ ጸሎትን አያይዞ የተደረገ ሥነ ሥርዓት እንደሆነ ለመረዳት ይቻላል። ቪዲዮው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ከተለያዩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ጋር በመሆን ለሰላም መቆሟን የሚያመለክት ነው። በተለይም የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ካህን በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተሳታፊ ሆነው ማየት ትልቅ ነገር ነው። ሊበረታታም የሚገባው እንቅስቃሴ ይመስላል።
ይህ ሁሉ መልካም ሆኖ ሳለ ቤተ ክርስቲያናችን ለዚህ የሰላም ጸሎት ተባባሪ ሆና ስትነሳ አንድ ማድረግ ያለባትን ነገር የረሳች ትመስላለች።  

Sunday, January 9, 2011

ሰበር ዜና - ከቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ኮሚቴ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ኮሚቴ በሜሪላን ከተማ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ አድርጎት በነበረው ስብሰባ ለመጪው የሰላምና የእርቅ ውይይት አስፈላጊ በሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች ላይ እንደሚወያይና ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ተጠብቆ ነበር። በዚህም መሠረት የደረሰን ዘገባ እንደሚያመለክተው የእርቅ ውይይቱን ስፍራ እና ጊዜ በተመለከተ ኮሚቴው ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ ስብሰባው በአሜሪካን ሀገር ከዐብይ ጾም መግቢያ በፊት እንዲሆን ወስኗል።  ባለፈው ዓመት ተደርጎ በነበረው የእርቅ ስብሰባ ዙሪያ የታዩትን ችግሮችን ለማስወገድ ይቻል ዘንድ ኮሚቴው የስብሰባውን ከተማና ቦታ እንዲሁም የስበሰባውን ጊዜ በዝርዝር እንደማይገለጽ ለመረዳት ችለናል። በአባቶች ስብሰባ ጊዜ ግራ አጋቢና ሃሳብ ከፋፋይ ግለሰቦች ድርሻ እንዳይኖራቸው አስፈላጊው ሁሉ ጥረት እንደሚደረግም የደረሰን ዘገባ ጨምሮ ያስረዳል።

የልደት በዓል ቡራኬ በስደት ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ


ብጹዕ አቡነ መልከጼዲቅ - ሊቀ ጳጳስ
በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

Friday, January 7, 2011

ጃንሜዳ በሎስ አንጀለስ

እንዳለፉት ዓመታት ሁሉ 2003 ዓ.ም. የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት በደመቀ ሁኔታ ለማክበር የሎስ አንጀለስ ድንግል ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በከፍተኛ ዝግጅት ላይ ትገኛለች። ይህ በዓል ከኢትዮጵያ ውጭ ለየት ባለና እጅግ በደመቀ ሁኔታ ላለፉት አሥራ አንድ ዓመታት በሎስ አንጀለስ ከተማ ሲከበር ቆይቷል።

በርከት ያሉ ታቦታት ባንድነት ወደ ጥምቀተ ባሕሩ የሚወርዱበት፣ ቁጥራቸው የበዛ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ካህናትን ዲያቆናት እና መዘምራን እንዲሁም ከተለያዩ ክፍላተ ሃገራት የሚመጡ በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ምዕመናን ስለሚገኙበት “ጃንሜዳ በሎስ አንጀለስ” በሚል ቅጽል ስም ይታወቃል።

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ !!!!

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ !!!!

Ethiopian Christ icon found 500 years on

An 15th century Ethiopian icon of the infant Christ child sitting on his mother's knee was discovered after it was cleaned by a British charity.


The central panel of the triptych had over the centuries become blackened with the sprinkling of perfume that the monks use as they worship.

Thursday, January 6, 2011

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ጉባኤ መግለጫ አወጣ።

በዚህ ሳምንት ለሁለት ቀናት በሜሪላንድ ስብሰባውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአንድነት ጉባኤ መግለጫ አወጣ።
  • የድጋፍ ጥሪ ለቤተ ክርስቲያንዋን ምእመናን ካህናት እና ሊቃውንት አስተላልፏል።
  • ለሰላሙ መሳካታ በማይበጁ አስተያየቶች ሕዝቡን ግራ እንዳያጋቡ ለዜና ማሰራጫዎች ጥሪ አቅርቧል።
  • ባዘጋጀው ድረ ገጽ (website) ላይ መረጃ እንደሚያስቀምጥ አስታውቋል።

Saturday, January 1, 2011

በአሌክሳንደሪያ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የቦምብ ጥቃት ደረሰባቸው ።

አክራሪ እስላሞች በኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ላይ እያደረሱ ያለው ጥቃት እንደቀጠለ ነው። ከኒው ዮርክ ፖስት ጋዜጣ ያገኘነውን ዜና ከዚህ በታች አስቀምጠንላችኋል   

Bomb hits Egypt church at New Year's Mass, 21 dead
BY MAGGIE MICHAEL
Associated Press
CAIRO (AP) -- A car exploded in front of a Coptic Christian church as worshippers emerged from a New Year's Mass in the Egyptian city of Alexandria early Saturday, killing at least 21 people, officials said.
After the blast, enraged Christians emerging from the church clashed with police and stormed a nearby mosque, prompting fights and volleys of stone throwing with Muslims, police and witnesses said - a sign of the sectarian anger that has been arising with greater frequency in Egypt.