የቅዱስ ሲኖዶስ
ክብር ግርማ ሞገስ
ጻድቅ ዜና ማርቆስ
ባርኩን በአጸደ ነፍስ።
ቀን ሲቆጠር ጊዜ
የመሮጡ አባዜ
ግባ መሬት ምሡ
አፈርን ሳይቀምሱ።
ሳምንት ሁለት ሳምንት ወራት እየበዛ
ያሉ እየመሰለን ዓመት እንደ ዋዛ።
ከእኛ ጋራ ሆነው ዘውትር ስናያቸው
አብረን ውለን አድረን ከቶ ማን ጠግቧቸው።
ቅዱስ አባታችን የተዋሕዶ ቤዛ
ዜና ከተለዩን ዓመት እንደዋዛ።
ብሩህ ገጽታዎን ሳናየው ብንቀር
እናት እንደ ሞተው ብሎናል ቅር ቅር።
ሺህ ዓመት ቢቆጠር ፍቅርን ድል አይነሳም
ዜና አባታችንን ምን ጊዜም አንረሳም።
እውነተኛ ባርያ ለጌታ የተገዛ
በቅፉ ካፈሩ ዓመት እንደዋዛ።
ከልጃቸው ከሰባኬ ወንጌል ሽመልስ ተሊላ
No comments:
Post a Comment